Telegram Group & Telegram Channel
"+" ቀዳም ሥዑር (የተሻረች ቅዳሜ) "+"

ቀዳም ስዑር ለምለም ቅዳሜ፣ ቅዱስ ቅዳሜ
ትባላለች፡፡ ቀዳም ሥዑር መባሉ ከወትሮው
ዕለታት በተለየ ይህችኛዋ ዕለት በጾም ስለምትታሰብ የተሻረች ቅዳሜ እንላታለን፡፡
ለምለም ቅዳሜ መባሏም ካህናቱ የምሥራች
አብሳሪ የሆነውን ቄጤማ ይዘው ወደ
ምእመናን ቤት ስለሚሔዱ ለምለም ቅዳሜ
ትባላለች፡፡ ቅዱስ ቅዳሜ መባሉም ቅዱስ
እግዚአብሔር አምላካችን በጥንተ ተፈጥሮ
ሃያ ሁለቱን ስነ ፍጥረታት የሚታዩትንና
የማይታዩትን፣ በእግር የሚሄዱትን እና በክንፍ
የሚበሩትን፣ በባሕር የሚዋኙትንና
በመጨረሻም ሰውን በአርአያውና በአምሳሉ
የፈጠረው በዕለተ ዐርብ ሲሆን ቅዳሜ ዕለት
ደግሞ ከሥራው ያረፈበት ዕለት ናት፡፡ በዘመነ
ሐዲስም የማዳን ሥራውን አከናውኖ በከርሰ
መቃብር አድሮ በአካለ ነፍስም ሲዖልን
በርብሮ ተግዘው የነበሩትን ነፍሳት ያወጣበት
ዕለት በመሆኑ ቅዱስ /ልዩ/ ቅዳሜ ተብላ
ተሰይማለች፡፡
ዕለቱ ዝርዘር አድርገን ስንመለከተውም ይህች
የመጀመሪያው ቅዳሜ ለእግዚአብሔር
የዕረፍት ዕለት ናት፤ እግዚአብሔር ሥነ
ፍጥረትን ፈጥሮ ስላረፈባት ሰንበት ዐባይ
(ታላቋ ሰንበት) ትባላለች (ዘፍ. 1፡3) ይህችን
ታላቋን ሰንበትም እንዲያከብሯት ሕዝበ
እግዚአብሔር የተባሉ እስራኤላውያን ታዘው
ነበር፡፡
ዕለተ ቀዳሚት (ሰንበት ዐባይ) በዘመነ
ሐዲስም የተለየ የድኅነት ሥራ
ተከናውኖባታል፡፡ ጥንት ሥነ ፍጥረትን
በመፍጠር ዕረፍት እንደተደረገባት ሁሉ
በሐዲስ ኪዳንም አዳምን ለማዳን ሕማምና
ሞት የተቀበለው ቸሩ አምላክ በሐዲስ
መቃብር አርፎባታል (ማቴ. 27፡61)፡፡
በዚህች ዕለት ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ በከርሰ መቃብር ዐርፎ የዋለባት
ዕለት በመሆኗ በምሥጢር ከሰንበት ዐባይ ጋር
ትገናኛለች፡፡ ቀዳም ስዑር (የተሻረች ቅዳሜ)
የተሰኘችውም በዓመት አንድ ቀን
ስለምትጾም ነው፡፡ እናቱ ቅድስት ድንግል
ማርያም፣ ወዳጆቹ ቅዱሳን ሐዋርያት ጌታ
ተላልፎ ከተሰጠበት ዕለት አንስተው ብርሃነ
ትንሣኤውን እስከሚያዩ ድረስ እህል ውኃ
በአፋቸው አልዞረም፡፡ ይመኩበትና ተስፋ
ያደርጉት የነበረ መምህራቸው በመቃብር
ስላረፈ ዕለቷን ነገረ ሞቱን በማሰብና
ትንሣኤውን በመናፈቅ በጾም አክብረዋታል፡፡
ከቅዱሳን ሐዋርያት ሲወርድ ሲወራረድ
በመጣው ትውፊት መሠረት ቅዱሳን
ሐዋርያት በሐዘን፣ በጾምና በጸሎት ዕለቷን
እንዳከበሯት ክርስቲኖችም የተቻላቸው
ከዓርብ ጀምረው በማክፈል፣ አሊያም ዓርብ
ማታ በልተው ቅዳሜን በመጾም የጌታን
ትንሣኤን ያከብራሉ፡፡
ቅዳሜ ጧት ምእመናኑና ካህናቱ ወደ ቤተ
ክርስቲን ይሰበሰባሉ፡፡ የጧቱ ጸሎት ሲፈጸም
”ገብረ ሰላመ በመስቀሉ” በመስቀሉ ሰላምን
መሠረተ፣ ሰላምን ፈጠረ፤ የምሥራች እየተባለ
በቤተ ክርስቲያን ለተሰበሰበው ሁሉ ቄጠማ
ይሰጣል፡፡ የምሥራች ምልክት ነው፡፡
ምእመናኑም እየሰነጠቁ በራሳቸው
ያስሩታል፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያን ላልመጡት
ምእመናንም ካህናት በየሰበካቸው ልብሰ
ተክህኖ ለብሰው መስቀልና ቃጭል ይዘው
ቄጠማውን የምሥራች እያሉ ያድላሉ፡፡
የዚህ የቄጠማው ታሪክ መነሻው የኖኅ ዘመን
ታሪክ ነው፡፡ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን
በጻድቁ ኖኅ ዘመን የነበሩ ሰዎች በማየ አይህ
ከጠፉ በኋላ የውኃውን መጉደል
እንድትመለከት የተላከች ርግብ የምሥራች
ምልክት የሆነ ለምለም ቄጠማ በአፏ ይዛ
ተመልሳለች፡፡ በዚህም የውኃው መጉደል፣
የቅጣቱ ዘመን ማለፍ ተረጋግጧል (ዘፍ. 9፡
1-29)፡፡
ቄጠማ ለጥፋት ውኃ መድረቅ የምሥራች
መንገሪያ እንደሆነው ሁሉ አሁንም በክርስቶስ
ሞት መተ ነፍስ ከሰው ልጆች ተወገደ ስትል
ቤተ ክርስቲያን ለልጆቿ ቄጠማ ታድላለች፡፡
ምእመናንም የምሥራች ተምሳሌት የሆነውን
ቄጠማ በግንባራቸው ያስሩታል፣ በጣታቸው
ቀለበት ያደርጉታል፡፡
የክርስቶስ ተከታዮች ሁሉ ከጨለማ
ወደሚደነቅ ብርሃን፣ ከሚያቃጥለው ዋዕየ
ሲዖል (የሲዖል ቃጠሎ) ወደ ልምላሜ ገነት፣
ጥንተ ማኅደራቸው መመለሳቸውን በዚህ
አኳኋን እየገለጡ በዓለ ትንሣኤን በቅድስት
ቤተ ክርስቲያን ያከብራሉ፡፡
ወንድሞቼና እህቶቼ እነሆ ስለ ቀዳም ስዑር
(የተሻረች ቅዳሜ) በማስመልከት ከስምዐ
ተዋሕዶ የስምዐ ጽድቅ ልዩ እትም ዘሰሙነ
ሕማማት፣ ማኅበረ ቅዱሳን፣ ሚያዝያ 2004፣
አዲስ አበባ ያገኘሁትን ስብከት
እንደሚከተለው ላካፍላችሁ፡፡
ቅዳሜ ቀዳም ሥዑር ይባላል፡፡ በዚች ዕለች
ከድሮው በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ
በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረችው
ቅዳሜ ትባላለች፡፡
የማትጾመዋ ቅዳሜ ስለምትጾም ስዑር /
የተሻረች/ ተብላለች በዓል መሻርን
አይመለከትም በቀዳም ሥዑር ሌሊት ሥርዓቱ
የሚጀመረው በመኀልየ ሰሎሞን ምንባብ
ነው፡፡ ማኀሌቱም እዝሉ እየተቃኘ
እየተመጠነ፣ እየተዘመመ እየተመረገደ
እየተጸፋ ያድራል፡፡ ጥዋት አቡን መዋሥዕት
ውዳሴ ማርያም ዜማ ተደርሶ ወለመልአከ
ሕይወትሰ ሰቀልዎ በሚለው ሰላም
ይጠናቀቃል፡፡በዚህ ዕለት ልብሰ ተክህኖ የለበሱ
ካህናትና ዲያቆናት ቄጤማ ተሸክመው ቃጭል
ሲያቃጨሉ መታየታቸው ዕለተ ትንሣኤውን
ለሚናፍቅ ምእመን ትልቅ ብስራት ነው፡፡
ለምለም ቅዳሜ፡- ካህናቱ ለምእመናን
ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት ስለሆነ
በዚህ ተሰይሟል፡፡ ቀጤማውንም ምእመናን
እስከ ትንሣኤ ሌሊት በራሳቸው ላይ
ያስሩታል፡፡
በቀዳም ስዑር ቀሳውስቱና ዲያቆናቱ
ቃጭል /ቃለዓዋዲ/ እየመቱ ገብረ ሰላመ
በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃደ የሚለውን
ያሬዳዊ ዜማ በመዘመር፤ ጌታ በመስቀሉ
ሰላምን እንደሰጠን እና ትንሣኤውንም
እንደገለጠልን በማብሰር፤ ቄጤማውን
ለምእመናን ይሰጣሉ፡፡
ምእመናኑም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት
የሚውል ገጸ በረከት ያቀርባሉ፡፡
ቄጤማውንም በራሳቸው ያስራሉ፡፡ ይህም
አይሁድ ጌታችንን እያሰቃዩ ሊሰቅሉት ባሉ ጊዜ
የእሾህ አክሊል ጭንቅላቱ ላይ ያሠሩበትን
ድርጊት የሚያስታውስ ነው፡፡
የቀጤማው አመጣጥና ምስጢርም
ከአባታችን ከኖኅ ታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡
ምድር በማየ አይኅ /በጥፋት ውኃ/ በጠፋችበት
ወቅት የኖኅ ታማኝ መልእክተኛ ርግብ
የውኃውን መጉደል ያበሰረችው ቀጤማ ይዛ
በመግባት ነው፡፡
ዛሬም ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች የኃጢአት
ውኃ ጐደለ፣ የኃጢአት ውኃ ጠፋ በክርስቶስ
ሞትና ትንሣኤ ነጻነት ተሰበከ ታወጀ በማለት
ካህናት ቄጠማ ይዘው ምእመናንን
ያበሥሩበታል፡፡
ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል፡፡ ቅዱስ ቅዳሜ መባሉ
ቅዱስ የሆነ እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ
ፍጥረታትን አከናውኖ ከፈጠረ በኋላ በዚህ ቀን
ከሥራው ሁሉ ያረፈበት ነው፡፡ በዘመነ ሐዲስ
ደግሞ የማዳን ሥራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው
በመቃብር ሲያርፍ፣ በነፍሱ ሲዖልን በርብሮ
ባዶዋን አስቀርቷታል፡፡ በዚያ ለነበሩት
ነፍሳትም የዘለዓለም ዕረፍትን ያወረሰበት
ዕለት ስለሆነ ከሌሎቹ ዕለታት የተለየ ዕለት
ለማለት ቅዱስ ቅዳሜ ተብሏል፡፡
ምእመናን ሆይ፣ በአጠቃላይ ሥርዓተ
ሕማሙን፤ ሰሙነ ሕማማት ብለው የተለየ
ሥርዓት አውጥተው አባቶቻችን ተግተው
ያቆዩልንን ሥርዓተ መላእክት ልንጠብቀውም
ልንጠቀምበት ይገባል፡፡ የዕለታቱን ክብርና
ስያሜ ከማወቅና ከመረዳት ጋር በዕለታቱ
የታዘዙትን ሃየማኖታዊ ግዴታዎችን መወጣት
ከሁላችንም ይጠበቃል፡፡
ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ እግዚአብሔር በሰላም
ከበዓሉ ረድኤት በረከት ያሳትፈን፣ አሜን፡፡



tg-me.com/rituaH/2277
Create:
Last Update:

"+" ቀዳም ሥዑር (የተሻረች ቅዳሜ) "+"

ቀዳም ስዑር ለምለም ቅዳሜ፣ ቅዱስ ቅዳሜ
ትባላለች፡፡ ቀዳም ሥዑር መባሉ ከወትሮው
ዕለታት በተለየ ይህችኛዋ ዕለት በጾም ስለምትታሰብ የተሻረች ቅዳሜ እንላታለን፡፡
ለምለም ቅዳሜ መባሏም ካህናቱ የምሥራች
አብሳሪ የሆነውን ቄጤማ ይዘው ወደ
ምእመናን ቤት ስለሚሔዱ ለምለም ቅዳሜ
ትባላለች፡፡ ቅዱስ ቅዳሜ መባሉም ቅዱስ
እግዚአብሔር አምላካችን በጥንተ ተፈጥሮ
ሃያ ሁለቱን ስነ ፍጥረታት የሚታዩትንና
የማይታዩትን፣ በእግር የሚሄዱትን እና በክንፍ
የሚበሩትን፣ በባሕር የሚዋኙትንና
በመጨረሻም ሰውን በአርአያውና በአምሳሉ
የፈጠረው በዕለተ ዐርብ ሲሆን ቅዳሜ ዕለት
ደግሞ ከሥራው ያረፈበት ዕለት ናት፡፡ በዘመነ
ሐዲስም የማዳን ሥራውን አከናውኖ በከርሰ
መቃብር አድሮ በአካለ ነፍስም ሲዖልን
በርብሮ ተግዘው የነበሩትን ነፍሳት ያወጣበት
ዕለት በመሆኑ ቅዱስ /ልዩ/ ቅዳሜ ተብላ
ተሰይማለች፡፡
ዕለቱ ዝርዘር አድርገን ስንመለከተውም ይህች
የመጀመሪያው ቅዳሜ ለእግዚአብሔር
የዕረፍት ዕለት ናት፤ እግዚአብሔር ሥነ
ፍጥረትን ፈጥሮ ስላረፈባት ሰንበት ዐባይ
(ታላቋ ሰንበት) ትባላለች (ዘፍ. 1፡3) ይህችን
ታላቋን ሰንበትም እንዲያከብሯት ሕዝበ
እግዚአብሔር የተባሉ እስራኤላውያን ታዘው
ነበር፡፡
ዕለተ ቀዳሚት (ሰንበት ዐባይ) በዘመነ
ሐዲስም የተለየ የድኅነት ሥራ
ተከናውኖባታል፡፡ ጥንት ሥነ ፍጥረትን
በመፍጠር ዕረፍት እንደተደረገባት ሁሉ
በሐዲስ ኪዳንም አዳምን ለማዳን ሕማምና
ሞት የተቀበለው ቸሩ አምላክ በሐዲስ
መቃብር አርፎባታል (ማቴ. 27፡61)፡፡
በዚህች ዕለት ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ በከርሰ መቃብር ዐርፎ የዋለባት
ዕለት በመሆኗ በምሥጢር ከሰንበት ዐባይ ጋር
ትገናኛለች፡፡ ቀዳም ስዑር (የተሻረች ቅዳሜ)
የተሰኘችውም በዓመት አንድ ቀን
ስለምትጾም ነው፡፡ እናቱ ቅድስት ድንግል
ማርያም፣ ወዳጆቹ ቅዱሳን ሐዋርያት ጌታ
ተላልፎ ከተሰጠበት ዕለት አንስተው ብርሃነ
ትንሣኤውን እስከሚያዩ ድረስ እህል ውኃ
በአፋቸው አልዞረም፡፡ ይመኩበትና ተስፋ
ያደርጉት የነበረ መምህራቸው በመቃብር
ስላረፈ ዕለቷን ነገረ ሞቱን በማሰብና
ትንሣኤውን በመናፈቅ በጾም አክብረዋታል፡፡
ከቅዱሳን ሐዋርያት ሲወርድ ሲወራረድ
በመጣው ትውፊት መሠረት ቅዱሳን
ሐዋርያት በሐዘን፣ በጾምና በጸሎት ዕለቷን
እንዳከበሯት ክርስቲኖችም የተቻላቸው
ከዓርብ ጀምረው በማክፈል፣ አሊያም ዓርብ
ማታ በልተው ቅዳሜን በመጾም የጌታን
ትንሣኤን ያከብራሉ፡፡
ቅዳሜ ጧት ምእመናኑና ካህናቱ ወደ ቤተ
ክርስቲን ይሰበሰባሉ፡፡ የጧቱ ጸሎት ሲፈጸም
”ገብረ ሰላመ በመስቀሉ” በመስቀሉ ሰላምን
መሠረተ፣ ሰላምን ፈጠረ፤ የምሥራች እየተባለ
በቤተ ክርስቲያን ለተሰበሰበው ሁሉ ቄጠማ
ይሰጣል፡፡ የምሥራች ምልክት ነው፡፡
ምእመናኑም እየሰነጠቁ በራሳቸው
ያስሩታል፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያን ላልመጡት
ምእመናንም ካህናት በየሰበካቸው ልብሰ
ተክህኖ ለብሰው መስቀልና ቃጭል ይዘው
ቄጠማውን የምሥራች እያሉ ያድላሉ፡፡
የዚህ የቄጠማው ታሪክ መነሻው የኖኅ ዘመን
ታሪክ ነው፡፡ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን
በጻድቁ ኖኅ ዘመን የነበሩ ሰዎች በማየ አይህ
ከጠፉ በኋላ የውኃውን መጉደል
እንድትመለከት የተላከች ርግብ የምሥራች
ምልክት የሆነ ለምለም ቄጠማ በአፏ ይዛ
ተመልሳለች፡፡ በዚህም የውኃው መጉደል፣
የቅጣቱ ዘመን ማለፍ ተረጋግጧል (ዘፍ. 9፡
1-29)፡፡
ቄጠማ ለጥፋት ውኃ መድረቅ የምሥራች
መንገሪያ እንደሆነው ሁሉ አሁንም በክርስቶስ
ሞት መተ ነፍስ ከሰው ልጆች ተወገደ ስትል
ቤተ ክርስቲያን ለልጆቿ ቄጠማ ታድላለች፡፡
ምእመናንም የምሥራች ተምሳሌት የሆነውን
ቄጠማ በግንባራቸው ያስሩታል፣ በጣታቸው
ቀለበት ያደርጉታል፡፡
የክርስቶስ ተከታዮች ሁሉ ከጨለማ
ወደሚደነቅ ብርሃን፣ ከሚያቃጥለው ዋዕየ
ሲዖል (የሲዖል ቃጠሎ) ወደ ልምላሜ ገነት፣
ጥንተ ማኅደራቸው መመለሳቸውን በዚህ
አኳኋን እየገለጡ በዓለ ትንሣኤን በቅድስት
ቤተ ክርስቲያን ያከብራሉ፡፡
ወንድሞቼና እህቶቼ እነሆ ስለ ቀዳም ስዑር
(የተሻረች ቅዳሜ) በማስመልከት ከስምዐ
ተዋሕዶ የስምዐ ጽድቅ ልዩ እትም ዘሰሙነ
ሕማማት፣ ማኅበረ ቅዱሳን፣ ሚያዝያ 2004፣
አዲስ አበባ ያገኘሁትን ስብከት
እንደሚከተለው ላካፍላችሁ፡፡
ቅዳሜ ቀዳም ሥዑር ይባላል፡፡ በዚች ዕለች
ከድሮው በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ
በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረችው
ቅዳሜ ትባላለች፡፡
የማትጾመዋ ቅዳሜ ስለምትጾም ስዑር /
የተሻረች/ ተብላለች በዓል መሻርን
አይመለከትም በቀዳም ሥዑር ሌሊት ሥርዓቱ
የሚጀመረው በመኀልየ ሰሎሞን ምንባብ
ነው፡፡ ማኀሌቱም እዝሉ እየተቃኘ
እየተመጠነ፣ እየተዘመመ እየተመረገደ
እየተጸፋ ያድራል፡፡ ጥዋት አቡን መዋሥዕት
ውዳሴ ማርያም ዜማ ተደርሶ ወለመልአከ
ሕይወትሰ ሰቀልዎ በሚለው ሰላም
ይጠናቀቃል፡፡በዚህ ዕለት ልብሰ ተክህኖ የለበሱ
ካህናትና ዲያቆናት ቄጤማ ተሸክመው ቃጭል
ሲያቃጨሉ መታየታቸው ዕለተ ትንሣኤውን
ለሚናፍቅ ምእመን ትልቅ ብስራት ነው፡፡
ለምለም ቅዳሜ፡- ካህናቱ ለምእመናን
ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት ስለሆነ
በዚህ ተሰይሟል፡፡ ቀጤማውንም ምእመናን
እስከ ትንሣኤ ሌሊት በራሳቸው ላይ
ያስሩታል፡፡
በቀዳም ስዑር ቀሳውስቱና ዲያቆናቱ
ቃጭል /ቃለዓዋዲ/ እየመቱ ገብረ ሰላመ
በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃደ የሚለውን
ያሬዳዊ ዜማ በመዘመር፤ ጌታ በመስቀሉ
ሰላምን እንደሰጠን እና ትንሣኤውንም
እንደገለጠልን በማብሰር፤ ቄጤማውን
ለምእመናን ይሰጣሉ፡፡
ምእመናኑም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት
የሚውል ገጸ በረከት ያቀርባሉ፡፡
ቄጤማውንም በራሳቸው ያስራሉ፡፡ ይህም
አይሁድ ጌታችንን እያሰቃዩ ሊሰቅሉት ባሉ ጊዜ
የእሾህ አክሊል ጭንቅላቱ ላይ ያሠሩበትን
ድርጊት የሚያስታውስ ነው፡፡
የቀጤማው አመጣጥና ምስጢርም
ከአባታችን ከኖኅ ታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡
ምድር በማየ አይኅ /በጥፋት ውኃ/ በጠፋችበት
ወቅት የኖኅ ታማኝ መልእክተኛ ርግብ
የውኃውን መጉደል ያበሰረችው ቀጤማ ይዛ
በመግባት ነው፡፡
ዛሬም ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች የኃጢአት
ውኃ ጐደለ፣ የኃጢአት ውኃ ጠፋ በክርስቶስ
ሞትና ትንሣኤ ነጻነት ተሰበከ ታወጀ በማለት
ካህናት ቄጠማ ይዘው ምእመናንን
ያበሥሩበታል፡፡
ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል፡፡ ቅዱስ ቅዳሜ መባሉ
ቅዱስ የሆነ እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ
ፍጥረታትን አከናውኖ ከፈጠረ በኋላ በዚህ ቀን
ከሥራው ሁሉ ያረፈበት ነው፡፡ በዘመነ ሐዲስ
ደግሞ የማዳን ሥራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው
በመቃብር ሲያርፍ፣ በነፍሱ ሲዖልን በርብሮ
ባዶዋን አስቀርቷታል፡፡ በዚያ ለነበሩት
ነፍሳትም የዘለዓለም ዕረፍትን ያወረሰበት
ዕለት ስለሆነ ከሌሎቹ ዕለታት የተለየ ዕለት
ለማለት ቅዱስ ቅዳሜ ተብሏል፡፡
ምእመናን ሆይ፣ በአጠቃላይ ሥርዓተ
ሕማሙን፤ ሰሙነ ሕማማት ብለው የተለየ
ሥርዓት አውጥተው አባቶቻችን ተግተው
ያቆዩልንን ሥርዓተ መላእክት ልንጠብቀውም
ልንጠቀምበት ይገባል፡፡ የዕለታቱን ክብርና
ስያሜ ከማወቅና ከመረዳት ጋር በዕለታቱ
የታዘዙትን ሃየማኖታዊ ግዴታዎችን መወጣት
ከሁላችንም ይጠበቃል፡፡
ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ እግዚአብሔር በሰላም
ከበዓሉ ረድኤት በረከት ያሳትፈን፣ አሜን፡፡

BY ርቱዓ ሃይማኖት


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/rituaH/2277

View MORE
Open in Telegram


ርቱዓ ሃይማኖት Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram announces Anonymous Admins

The cloud-based messaging platform is also adding Anonymous Group Admins feature. As per Telegram, this feature is being introduced for safer protests. As per the Telegram blog post, users can “Toggle Remain Anonymous in Admin rights to enable Batman mode. The anonymized admin will be hidden in the list of group members, and their messages in the chat will be signed with the group name, similar to channel posts.”

Launched in 2013, Telegram allows users to broadcast messages to a following via “channels”, or create public and private groups that are simple for others to access. Users can also send and receive large data files, including text and zip files, directly via the app.The platform said it has more than 500m active users, and topped 1bn downloads in August, according to data from SensorTower.ርቱዓ ሃይማኖት from it


Telegram ርቱዓ ሃይማኖት
FROM USA